Monday, July 27, 2015

የጌታ እራት ዛሬ ለእኛ ምንድነው ? ክፍል ስድስት 2ኛ ) The Consubstantiation View

የጌታ እራት ዛሬ ለእኛ ምንድነው ?


ክፍል ስድስት


2ኛ ) The Consubstantiation View



ሁለተኛው የዕይታ ነጥብ የተገለጸው በማርቲን ሉተር ነው  ይህም የጌታ ሥጋና ደም በእውነት በእኛና በእኛ ውስጥ ማለት ባዘጋጀነው ዳቦና ወይን ውስጥ ይገኛል ጥንተ ነገሩ በእውነተኛነት ወደ ክርስቶስ ሥጋና ደም የሚለወጥ አይደለም ነገር ግን በአንድ ዓይነት መንገድ ሙቀቱ በጥንተ ነገር ውስጥ ይገኛል ስለዚህ በሉተራን ሁናቴ ይህ ጉዳይ ሁልጊዜ የሚጠራው Consubstantiation በመባል ነው ሁኔታው ክርስቶስ በእውነተኛነት በእራት ውስጥ ስላለ ይህንን በመገንዘብ ቅዱስ ቁርባኑን ለመቀበል ሊያበረታታ የሚችል ነው ነገር ግን የጌታን ቃል ቅርጽና መልክ መጠቀም ለማግኘት ያልቻለ ነው ከራሱ ከክርስቶስ ይልቅ በዳቦውና በወይኑ ላይ ሥዕሉን በማድረግ አትኩሮት የሰጠና ያዘነበለ ነው ይሁን እንጂ መጽሐፍቅዱሳችን የሚለን ይህንን ነው የእግዚአብሔር መንግሥት ጽድቅና ሰላም በመንፈስ ቅዱስም የሆነ ደስታ ናት እንጂ መብልና መጠጥ አይደለችምና ይለናል ሮሜ 14 17 እንደገናም መብል ግን ወደ እግዚአብሔር አያቀርበንም፤ ባንበላም ምንም አይጎድለንም ብንበላም ምንም አይተርፈንም ይለናል 1 ቆሮንቶስ 8 8 ከዚህም ሌላ እንግዲህ በመብል ወይም በመጠጥ ወይም ስለ በዓል ወይም ስለ ወር መባቻ ወይም ስለ ሰንበት ማንም አይፍረድባችሁ እነዚህ ሊመጡ ያሉት ነገሮች ጥላ ናቸውና፥ አካሉ ግን የክርስቶስ ነው በማለትም ይናገራል ቆላስያስ 2 16 እና 17 መጽሐፍቅዱሳችን እንደሚያስተምረን የምንባርከው የበረከት ጽዋ ከክርስቶስ ደም ጋር ኅብረት ያለው አይደለምን ? የምንቆርሰውስ እንጀራ ከክርስቶስ ሥጋ ጋር ኅብረት ያለው አይደለምን ? አንድ እንጀራ ስለ ሆነ፥ እኛ ብዙዎች ስንሆን አንድ ሥጋ ነን፤ ሁላችን ያን አንዱን እንጀራ እንካፈላለንና  በሥጋ የሆነውን እስራኤል ተመልከቱ፤ መሥዋዕቱን የሚበሉ የመሠዊያው ማኅበረተኞች አይደሉምን ? ይለናልና የምንቆርሰው እንጀራም ሆነ የምንወስደው የበረከት ጽዋ ይህንን ቃሉን ለተረዳን ለእኛ ትልቅ ትርጉም አለው ከጌታ ጋር ባለን ነገርና የእርስ በእርስ ግንኙነታችን አንድነታችንን የምናረጋግጥበት ነው ስለዚህ እንዲሁ የምንወስደው እንጀራም ሆነ የበረከት ጽዋ የለም እንደገናም የእግዚአብሔር ቃል የማይመሰክርልንን ቅርጽና መልክም የማይሰጠንና ያላስያዘልንን እራት የጌታ እራትም ሆነ የበረከት ጽዋ ነው ስንል አንወስድም ማንኛውንም ነገር የምናደርገው በዘፈቀደ ሳይሆን እንደ እግዚአብሔር ቃል ስለሆነ የእግዚአብሔርን ቃል ብቻ ተከትለን እናደርጋለን 1 ጴጥሮስ 4 11  2 ጴጥሮስ 1 19 የምንቆርሰው እንጀራም ሆነ የምንወስደው የበረከት ጽዋ ከክርስቶስ ጋር ኅብረት ኖሮት ለእኛም ኅብረትን  የማይሰጠን ከሆነ እንደገናም የእርስ በእርስ ኅብረታችንንም ጭምር የማያጸናልን ከሆነ ያው የተለመደው በተፈጥሮ የምናውቀው  ዳቦና ወይን ነው ከዚህ የተለየ ትርጉምም ልንሰጠው አንችልም መጽሐፍቅዱሳችን ግን የምንቆርሰው እንጀራም ሆነ የበረከት ጽዋ ከክርስቶስ ጋር ኅብረት ያለው ስለሆነ ይህንን እንጀራም ሆነ የበረከት ጽዋ ስንካፈል በጥንቃቄ መሆን እንዳለበት ቃሉ ይነግረናል ለዚህም ነው ማንም የራበው ቢኖር ለፍርድ እንዳትሰበሰቡ በቤቱ ይብላ የቀረውንም በመጣሁ ጊዜ እደነግጋለሁ የሚለን 1 ቆሮንቶስ 11 27 _ 34 ከክርስቶስ ጋር ያልተገናኘን ኅብስትና ወይን እኛ አማኞች እንደ ቃሉ እንጂ በሉተራን ዓይን ተመልክተን ውሳኔ የምንሰጥበት አይሆንም ከክርስቶስ ጋር ያልተገናኘ ኅብስትና ወይን ክርስቶስ በእውነተኛነት በእራት ውስጥ ስላለ በአንድ ዓይነት መንገድ ሙቀቱ በጥንተ ነገር ውስጥ ይገኛል ብለን አናስብም የጌታን ቃል ቅርጽና መልክ መጠቀም ለማግኘት ያልቻለ እንደገናም ከራሱ ከክርስቶስ ይልቅ በዳቦውና በወይኑ ላይ ሥዕሉን በማድረግ አትኩሮት የሰጠና ያዘነበለ በመሆኑ ተራ ዳቦና ወይን ነው ከምንለው ውጪ ሌላ ትርጉም አንሰጠውም ወገኖቼ በዚህ ቃል ተባረኩ እያልኩኝ ይህንን ትምህርት እንድታነቡ እጋብዛለሁ በክፍል ሰባት ትምህርት እስክንገናኝ የጌታ ጸጋና ሰላም ከሁላችን ጋር ይሁን በማለት እሰናበታለሁ ተባረኩልኝ ለዘላለም



Joshua Breakthrough Renewal Teaching and Preaching Ministry አገልጋይና ባለ ራዕይ

ቀሲስ ዮናስ ጌታነህ


No comments:

Post a Comment