Thursday, August 6, 2015

የጌታ እራት ለእኛ ምንድነው ? ለዛሬ ያለው ትርጉም Meaning for today ክፍል ዘጠኝ

የጌታ እራት ለእኛ ምንድነው ?



ለዛሬ ያለው ትርጉም




Meaning for today  




ክፍል ዘጠኝ








ዛሬን ስንጠይቅ ለክርስቲያኑ የጌታ እራት ትርጉሙ እንዴት ነው ? ሦስት የተያያዙ ሃሳቦች ለሃላፊ ጊዜ ለአሁን ጊዜና ለወደፊት ጊዜ ሊጠቅሙ የሚችሉ ሲሆኑ እነርሱም ተያይዘው ያሉና  የተገናኙም ናቸው


1ኛየጌታ እራት የጌታን መታሰቢያ ጊዜ    የምናስታውስበት ነው ጌታም እንዲህ ሲል ትዕዛዝ ሰጥቷል<< Do this in remembrance of me  >> የሉቃስ ወንጌል 22 19 1 ቆሮንቶስ 11 24   _  25 ይህ ለመኖርያችን ዋጋ ለመክፈል በአዕምሮ ወይም በሥጋ የምንጨነቅበት ሳይሆን ግሩምና ድንቅ የሆነውን የጌታን የማዳን ሕይወትና አገልግሎት ለማስታወስ ነው ይህ የጌታ እራት ጥልቅ የሆነውን ምሥጋናና አድናቆት ኢየሱስ ክርስቶስ ለእኛ ስላደረገልን ለመግለጽ ትልቅ በዓል ወይንም በእንግሊዘኛው Occasion ነው

     በአይሁድ የፋሲካ እራት ጊዜ የዕብራውያን ከግብጽ ባርነት ነጻ መውጣት የታወጀ አንድ ደረጃም ወደፊት የሄደ ነበረ በዘጸአት 12 26 እና 27 ላይ እንዲህ የሚል ቃል ተጽፎ እናገኛለን እንዲህም ይሆናል፤ ልጆቻችሁ፦ ይህ አምልኮ ለእናንተ ምንድር ነው ?  ባሉአችሁ ጊዜ፥ እናንተ፦ በግብፅ አገር በእስራኤል ልጆች ቤቶች ላይ አልፎ ግብፃዊያንን በመታ ጊዜ፥ ቤቶቻችንን ያዳነ የእግዚአብሔር የማለፉ መሥዋዕት ይህች ናት ትሉአቸዋላችሁይለናል  በመሆኑም በዚህ በሐዲስ ኪዳኑ የጌታ እራት ደግሞ ክርስቲያኑ ከኃጢአት ነጻ መውጣቱን ፣ ከሞት ሥቃይ መከራ በአካልና በአዕምሮም  ሳይቀር ፋሲካችን በሆነው ክርስቶስ እንደገናም ነጻ መውጣቱንና መላቀቁንም ጭምር ያውጃል( 1 ቆሮንቶስ 5 7 1 ቆሮንቶስ 11 26 )


2ኛሁለተኛው የጌታ እራት ጊዜ ፦ብርታት የማግኘት ጉልበት የማግኘት የመታደስ ጊዜ የመተሳሰርና የቁርባን ጊዜ  ነው እንደ ተሳትፎአችን መጠን የኢየሱስ ሞትና ትንሣኤ ትርፉ ሕይወትን መስጠት ነው( ሮሜ 5 10 1 ቆሮንቶስ 10 16 ) ስለዚህ በክርስቶስ ትንሣኤ ባለ መንፈስ ውስጥ ሥልጣንን አግኝተን እንመገባለን እናድጋለን ዮሐንስ ዊስሊ ይህንን ጥንካሬ ያውቃል በአማካኝ በየአራት ወይም አምስት ቀን በረጅም ጊዜና ፍሬያማ ሥራው ወይንም የሕይወት ታሪኩ ቁርባኑን የወስዳል ያለ ጌታ እራት እግዚአብሔር ሥልጣንን አይሰጠንም ነገር ግን ለእኛ የጌታ እራት ተቋም አዘጋጅቷል እንደገናም ለግንኙነት መንገድና ዘዴ ጸሎትንና የእግዚአብሔር ቃል መስማትን ሰይሟል የዮሐንስ ዊስሊ መመርያ ሁልጊዜ ጠንከር ያለ ፣ ማሰብንና ማመዛዘንን የተገባን እንድንሆን አስችሎናል


3ኛ) ሦስተኛውና የመጨረሻው የጌታ እራት ጊዜ ቃልኪዳንን የማደስ እና ተስፋ የማድረግ ጊዜ ነው ነገር ግን ራሳችንን ቃል በቃል ማረጋገጥና የጥራት ሙከራ ወይንም ፈተና ማድረግ አለብን የጌታን እራት ተካፍለን የምንበላበት አኳኋን ዋጋ ያለው ነው( 1 ቆሮንቶስ 11 28 እና 29 ) እንደገናም የእርሱ ሕዝቦች ሙሉ በሆነ የመታደስ ተስፋ ለክርስቶስ የተሰጠንበትን እናድሳለን እርሱ እስኪመጣ ድረስ ( 1 ቆሮንቶስ 11 26 ) ክርስቶስ ከተመለሰ በኋላ በእርሱ መንግሥት ውስጥ በእርሱ አካላዊ መገኘት ከእርሱ ጋር ተካፍለን እንበላለን ( የማቴዎስ ወንጌል 26 29 ) የተወደዳችሁ ወገኖች የጌታን እራት ትምህርታችንን በዚህ የክፍል ዘጠኝ ትምህርት በማጠቃለል እንደመድማለን ጥያቄ ወይንም አስተያየት ካላችሁ በዚሁ በፌስቡክ አድራሻችን በብሎጎቻችንና በጎግል አድራሻችን ልትልኩልን ትችላላችሁ ወገኖቼ ትምህርቱ ከክፍል አንድ እስከ ክፍል ዘጠኝ ድረስ በየተራ የተለቀቀ ስለሆነ ሕይወታችንን የሚመሠርት ነውና በመደጋገም እንድትከታተሉት እንድታጠኑትም ማሳሰብ እወዳለሁ ለሌሎችም ወገኖቻችን ይጠቀሙ ዘንድ ሼር አድርጉት በተረፈ በሚቀጥሉት ሌሎች አዳዲስ ትምህርቶችና የትምህርት አርዕስቶች እስክንገናኝ ሰላም ሁኑ በማለት የምሰናበታችሁ



Joshua Breakthrough Renewal Teaching and Preaching Ministry አገልጋይና ባለ ራዕይ

ቀሲስ ዮናስ ጌታነህ ነኝ

God bless all People of God amen and amen.

No comments:

Post a Comment