Monday, September 7, 2015

እውነተኛ የጌታ ተከታይ ማነው ? Who are God`s True Followers? ክፍል ሁለት

እውነተኛ የጌታ ተከታይ ማነው ?


Who are God`s True Followers?


ክፍል ሁለት


እነዚህ በጉን ይወጋሉ በጉም የጌቶች ጌታና የነገሥታት ንጉሥ ስለሆነ እነርሱን
ድል ይነሣል ከእርሱም ጋር ያሉ የተጠሩና የተመረጡ የታመኑ ደግሞ ድል ይነሳሉ

ራዕይ 17 14




እነዚህ በጉን የሚወጉ ቢሆንም በጉ ግን የጌቶች ጌታና የነገሥታት ንጉሥ ስለሆነ እነርሱን ድል ይነሣል በመሆኑም ይህ የሚያሳየን እንግዲህ የበጉን ሉዓላዊነት እና ሁሉን ቻይነት በአጽንዖት የሚገልጽ መሆኑን ነው በዘዳግም 10 17 ላይ እንግዲህ አምላካችሁ እግዚአብሔር የአማልክት አምላክ የጌቶችም ጌታ ታላቅ አምላክ ኃያልም የሚያስፈራም በፍርድ የማያደላ መማለጃም የማይቀበል ነውና እናንተ የልባችሁን ሸለፈት ግረዙ ከእንግዲህ ወዲህም አንገተ ደንዳና አትሁኑ ይለናል በትንቢተ ዳንኤል 2 47 ላይ ደግሞ ንጉሡም ዳንኤልን ይህን ምሥጢር ትገልጥ ዘንድ ተችሎሃልና በእውነት አምላካችሁ የአማልክት የነገሥታትም ጌታ ምሥጢርም ገላጭ ነው ብሎ ተናገረው ይለናል በ1ኛ ጢሞቴዎስ 6 15 ላይ ደግሞ ያንም መገለጡን በራሱ ጊዜ ብፁዕና ብቻውን የሆነ ገዢ የነገሥታት ንጉሥና የጌቶች ጌታ ያሳያል እርሱ ብቻውን የማይሞት ነው ማንም ሊቀርበው በማይችል ብርሃን ይኖራል አንድ ሰው እንኳ አላየውም ሊያየውም አይቻለውም ለእርሱ ክብርና የዘላለም ኃይል ይሁን አሜን ይለናል ስለዚህ ጌታችን እንደዚህ ዓይነት ጌታ ስለሆነ ሉዓላዊና አሸናፊ ጌታ  ሁሉን ቻይ የሆነም ጌታ ነው ከዚህም ሌላ በራዕይ መጽሐፍ ላይ አስደናቂ የሆነ ቃል እናገኛለን እርሱም እንዲህ ይላል ሰማይ ተከፍቶ አየሁ እነሆም አምባ ላይ ፈረስ የተቀመጠበትም የታመነና እውነተኛ ይባላል በጽድቅም ይፈርዳል ይዋጋልም ዓይኖቹም እንደ እሳት ነበልባል ናቸው በራሱ ላይም ብዙ ዘውዶች አሉ ከእርሱም በቀር አንድ እንኳ የማያውቀው የተጻፈ ስም አለው በደምም የተረጨ ልብስ ተጐናጽፎአል ስሙም የእግዚአብሔር ቃል በሰማይም ያሉት ጭፍራዎች ነጭና ጥሩ ቀጭን የተልባ እግር ልብስ ለብሰው በአምባላዮች ፈረሶች ተቀምጠው ይከተሉት ነበር አሕዛብንም ይመታበት ዘንድ ስለታም ሰይፍ ከአፉ ይወጣል እርሱም በብረት በትር ይገዛቸዋል እርሱም ሁሉን የሚገዛ የእግዚአብሔርን የብርቱ ቁጣውን ወይን መጥመቅያ ይረግጣል በልብሱና በጭኑም የተጻፈበት የነገሥታት ንጉሥና የጌታዎች ጌታ የሚል ስም አለው ይለናል ራዕይ 19 11 _ 16 ታድያ ከዚህ ድል ነሺ ጌታ የተነሳ የእኛም ሕይወት በድል የተሞላ ነው  ምክንያቱም ከእርሱም ጋር ያሉ የተጠሩና የተመረጡ የታመኑም ደግሞ ድል ይነሣሉ ይለናልና ስለዚህ እውነተኛ የጌታ ተከታዮች የተጠሩ የተመረጡ የታመኑ ተብለው የተጠሩ ብቻ ሳይሆኑ እነርሱም የዚህ ጌታ ነገር ገብቶአቸው መጠራታቸውን ያጸኑ ይህንኑ ጌታ የመረጡና በታማኝነትም ከእርሱ ጋር ያሉ ናቸው ጌታ እግዚአብሔር የእያንዳንዳችንን እድል ፈንታ እንደዚህ ያድርገው መጽሐፍ ሲናገር በማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ 7 21 ላይ በሰማያት ያለውን የአባቴን ፈቃድ የሚያደርግ እንጂ ጌታ ሆይ ጌታ ሆይ የሚለኝ ሁሉ መንግሥተ ሰማያት የሚገባ አይደለም ይለናል አያይዞም በዚሁ በማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ 7 23 ላይ ደግሞ የዚያን ጊዜም ከቶ አላውቃችሁም እናንተ አመጸኞች ከእኔ ራቁ ብዬ እመሰክርባቸዋለሁ ይለናል ኢየሱስ ክርስቶስ እውነተኛ ነው እርሱ ተነስቶአል በዓለምም ላይ ተጽዕኖን አምጥቷል አብዛኛው ሰው የኢየሱስ ክርስቶስ የስሙ ቤተሰብ ነው ነገር ግን ምን ያህሉ ያውቀዋል ? እርሱ ያስተማረውና የእርሱ ተልዕኮ ምን ነበር ? የእርሱስ እውነተኛ ተከታዮች ልዩነታቸው ምንድርነው ?ማንስ ነው እርሱን በትክክል የሚወክል?  መጽሐፍቅዱሳችን በማቴዎስ ወንጌል 22 14 ላይ የተጠሩ ብዙዎች የተመረጡ ግን ጥቂቶች ናቸውና ይለናል በዮሐንስ ወንጌል 16 33 ላይ ደግሞ በእኔ ሳላችሁ ሰላም እንዲሆንላችሁ ይህን ተናግሬያችኋለሁ በዓለም ሳላችሁ መከራ አለባችሁ ነገር ግን አይዞአችሁ እኔ ዓለምን አሸንፌዋለሁ ይለናል   ስለዚህ ከተጠሩት ብቻ ሳይሆን ከተመረጡት ወገን ሆነን በዓለም ሳለን መከራ ቢሆንብንም ክርስቶስ ግን ዓለምን አሸንፎታልና በዚህ ደስ ይበለን ዋናው ነገር በክርስቶስ ሳለን ሰላም እንዲሆንልን ጌታ ተናግሮናል ኢየሱስ ቤተክርስቲያኔን እገነባለሁ አለ የማቴዎስ ወንጌል 16 18 የግሪኩ ቃል ቤተክርስቲያንን ሲተረጉመው ኤክሌሽያ ይለዋል ትርጉሙም  Assembly ማለት ሲሆን ስብሰባ መሰብሰብ ማለትን ያመለክታል በትክክልና በግልጥ ሲነገር ደግሞ " A calling out "or " called out ones " ተጠርቶ የወጣ ወይንም አንድ ጊዜ ተጠርቶ የወጣ ማለትን የሚያመለክት ነው The meaning of the word Akklesia is " from ek " out of " and klesis a calling (kaleo, "to call ")ማለት ነው  በሐዋርያት ሥራ 19 39 ላይ Assembly ወይንም ስብሰባ የሚለውን ቃል ሲተረጉመው ስለሌላ ነገር እንደሆነ ግን አንዳች ብትፈልጉ በተደነገገው ጉባኤ ይፈታል ይለናል የሐዋርያት ሥራ 19 39 የዕብራውያን መጽሐፍ የአማኞችን አካልነት የበኩራት ማኅበርና የቤተክርስቲያን ጠቅላላ ስብሰባ ይለዋል ዕብራውያን 12 23 ከዚህ የተነሳ ቤተክርስቲያን የሕያው የእግዚአብሔር ቤተክርስቲያን የእውነት ዓምድና መሠረት የሆነች ቤተክርስቲያን ናት 1 ጢሞቴዎስ 3 15 Paul describes it as " The Church of the living God the Pillar and ground of the truth "


ጌታ እግዚአብሔር የምናነበውን ቃል ይባርክልን


Joshua Breakthrough Renewal Teaching and Preaching Ministry
አገልጋይና ባለ ራዕይ

ቀሲስ ዮናስ ጌታነህ ነኝ

ተባረኩልኝ ለዘላለም



Friday, September 4, 2015

Joshua Tehadso: የትምህርት ርዕስ የሕይወት መለወጥ Life transformation ...

Joshua Tehadso: የትምህርት ርዕስ የሕይወት መለወጥ Life transformation ...: የትምህርት ርዕስ የሕይወት መለወጥ Life transformation ክፍል አንድ የተወደዳችሁ ወገኖች ዛሬ ወደ እናንተ የቀረብኩት አዲስ እና ተከታታይ የሆነ ...

የትምህርት ርዕስ የሕይወት መለወጥ Life transformation ክፍል አንድ

የትምህርት ርዕስ


የሕይወት መለወጥ



Life transformation


ክፍል አንድ


የተወደዳችሁ ወገኖች ዛሬ ወደ እናንተ የቀረብኩት አዲስ እና ተከታታይ የሆነ ትምህርት ይዤ ነው በተለያዩ ንዑሳን አርዕስቶች የሚቀርቡ ተከታታይ የሆኑ ሃሳቦች ያሏቸው ትምህርቶች ናቸው ከዛሬው የትምህርት ክፍለ ጊዜ በመጀመር እንግዲህ እንደሚገባ በማስተዋል እንድትከታተሉአቸውና እንድትጠቀሙባቸው በጌታ ፍቅር ለማሳሰብ እወዳለሁ ወደ  ዛሬው የትምህርት ክፍል ስመለስ በሐዋርያት ሥራ 15 3 ላይ  ቤተክርስቲያኑም በመንገድ እየረዳቸው እነርሱ የአሕዛብን መመለስ እየተረኩ በፊንቄና በሰማርያ አለፉ ወንድሞችንም ሁሉ እጅግ ደስ አሰኙአቸው ይለናል እንደገናም በደረሱም ጊዜ ቤተክርስቲያኑን ሰብስበው እግዚአብሔር ከእነርሱ ጋር ያደረገውን ሁሉ ለአሕዛብም የሃይማኖትን ደጅ እንደከፈተላቸው ተናገሩ በማለትም የእግዚአብሔር ቃል ይናገራል የሐዋርያት ሥራ 14 27 የሕይወት ለውጥ የአንድ ጊዜ ብቻ ሳይሆን የሁል ጊዜ ነው ለዚህም ነው መጽሐፍቅዱሳችን እኛም ሁላችን በመጋረጃ በማይከደን ፊት የጌታን ክብር እንደ መስታወት እያብለጨለጭን መንፈስ ከሚሆን ጌታ እንደሚደረግ ያን መልክ እንመስል ዘንድ ከክብር ወደ ክብር እንለወጣለን የሚለን 2 ቆሮንቶስ 3 18 በመሆኑም የአሕዛብን የጅማሬ ለውጥ ስንመለከት አሕዛብ መለወጥን ያደረጉት ቃሉን ሰምቶ በማመንና በመመለስ ነው ቃሉን ሰምተን ስናምን የእግዚአብሔር ቃል ይመልሰናል በሕይወታችንም ላይ ለውጥ እንድናደርግ ያስችለናል ለዚህም ነው በዚሁ በሐዋርያት ሥራ 14 27 ላይ  በደረሱም ጊዜ ቤተክርስቲያኑን ሰብስበው እግዚአብሔር ከእነርሱ ጋር ያደረገውን ሁሉ ለአሕዛብም የሃይማኖትን ደጅ እንደከፈተላቸው ተናገሩ በማለት የተናገረን እንግዲህ የሃይማኖትን ደጅ እንደከፈተላቸው ተናገሩ ሲለን በቃሉ ሊናገረን የወደደው የእምነትን በር እንደከፈተላቸው ተናገሩ በማለት ነው የእምነት በር ማለትም የማመን በር የሚከፈተው ቃሉን ብቻ አምነው ሊድኑና መንገዳቸውንም በቃሉ መሠረት ሊለውጡ ለወደዱ ሰዎች ነው በመሆኑም አሕዛብ ቃሉን አምነው መንገዳቸውንም በቃሉ ሊለውጡ ስለወደዱ ጌታ እግዚአብሔር የእምነትን በር ከፈተላቸው ከዚህ የተነሳ ማመንና መዳን መለወጥም ሆነላቸው ወገኖቼ በዚህ የተከፈተ የማመን በር ነው ወደ እግዚአብሔር መንግሥትም መግባት የሚቻለው ይሄ የማመን በር ደግሞ ከመዳን ባሻገር ለመለወጥ ለማደግና ክርስቶስንም ለመምሰል ጥርጊያ መንገድን የሚከፍት ነው ማመናችን ከጊዜ ወደ ጊዜ በእግዚአብሔር ቃል ከፍ እያለ ሲመጣ መለወጣችንና ማደጋችን ክርስቶስንም መምሰላችን በዚያው ልክ ክፍ እያለና እየጨመረ ይመጣል ታድያ ሰው ሲለወጥ ወይም ሲዛወር ተለወጠ ይባላል ለመለወጥ ግን በቅድሚያ አዕምሮን መክፈት የመጽሐፉንም ቃል ለመነጋገርና ለመስማት ፈቃደኛ መሆንን ይጠይቃል ያን ጊዜ የቃሉን እውነት መረዳት ይጀመራል እግዚአብሔር እንድንለወጥ መጽሐፉንም እንድንረዳ ይጋብዘናል የምንከተለው የመረጥነውን ነው የምናደርገው የሰማነውን ያየነውን ነው መለወጥ ሕይወትን መምረጥ ነው በዘዳግም 30 19 ላይ በፊታችሁ  ሕይወትንና ሞትን በረከትንና መርገምን እንዳስቀመጥኩ እኔ ዛሬ ሰማይንና ምድርን በአንተ ላይ አስመሰክራለሁ እንግዲህ አንተና ዘርህ በሕይወት ትኖሩ ዘንድ ሕይወትን ምረጥ እያለ ይናገራል በሐዲስ ኪዳንም ጌታ ኢየሱስ ማርያምን ሕይወትን መርጣ ቃሉን ልትሰማ በዚሁ ጌታ እግር ሥር በመቀመጧ መልካም  ዕድልን መርጣለች ከእርሷም አይወሰድባትም ነው ያለው  ማርታን ግን ማርታ ማርታ በብዙ ነገር ትጨነቂያለሽ ትታወኪማለሽ የሚያስፈልገው ግን ጥቂት ወይም አንድ ነገር ነው በማለት ተናገራት የሉቃስ ወንጌል 10 38 _ ፍጻሜ ትልቁ መልካም ዕድል ቃሉን ከመስማት የሚገኝ የሕይወት ምርጫ ነው እዚህ ምርጫ ውስጥ ገብተው ሕይወትን ያገኙ ደግሞም ይህን የምርጫቸውን ዕድል ተጠቅመው በዚህ የሕይወት ከፍታና ቃሉንም የመስማት አቅም ወደፊት ለሄዱ፣ ሊሄዱም ለወሰኑና በመሄድም ላይ ላሉ ሰዎች  ሕይወት ለእነርሱ የምርጫ ጉዳይ ብቻ ሳይሆን እየበዛና እየተትረፈረፈ የሚሄድ  ከእነርሱም  የማይወሰድ ነው እንደገናም ጌታ እግዚአብሔር የሰው ልጆችን ትክክለኛውን ምርጫ እንዲመርጡ ያበረታታል እንጂ ማንንም ፎርስ አያደርግም  He clearly encourages human beings to" choose life " መለወጥም የአንድ ጊዜ ሂደት ብቻ ሳይሆን ፕሮሰስ ነው ጌታ እግዚአብሔር በምናነበው ቃል ወደ እያንዳንዳችን ይምጣና ሕይወታችንንም ይለውጥ ተባረኩልኝ ቅዱሳን

Joshua Breakthrough Renewal Teaching and Preaching Ministry አገልጋይና ባለ ራዕይ

ቀሲስ ዮናስ ጌታነህ ነኝ