Friday, April 3, 2015

የሚመራ መፈለግ Seeking guidance ክፍል ሁለት ለእግዚአብሔር ሕግ መታዘዝ አንዱና ዋናው የቤተክርስቲያን ጠባይ ነው

የሚመራ መፈለግ


Seeking guidance


ክፍል ሁለት



ለእግዚአብሔር ሕግ መታዘዝ አንዱና ዋናው የቤተክርስቲያን ጠባይ ነው



የተወደዳችሁ ወገኖች በቃሉ አገልጋዮችም ይሁን በቤተክርስቲያን አገልግሎት ወደ ቃሉ ስንመራና የእግዚአብሔርን ቃል ስናውቅ የእግዚአብሔርን ቃል ለመታዘዝ እንነሳለን ሐዋርያው ጳውሎስ ለእግዚአብሐር ሕግ በመታዘዝ ምክንያት የሚገኘውን ጥቅም እንዲህ ሲል ይገልጸዋል ነገር ግን አስቀድማችሁ የኃጢአት ባሪያዎች ከሆናችሁ፥ ለተሰጣችሁለት ለትምህርት ዓይነት ከልባችሁ ስለ ታዘዛችሁ፥ ከኃጢአትም አርነት ወጥታችሁ ለጽድቅ ስለ ተገዛችሁ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን ሮሜ 6 17 እና 18 የሮሜ ክርስቲያኖች ከኃጢአት ነጻነት ወጥተው የጽድቅ ባርያዎች ሆነዋል ታድያ እንዲህ እንዲሆኑ ያስቻላቸው ነገር ምንድርነው ? ስንል ከዚህ በፊት የኃጢአት ባሮች ነበሩ ነገር ግን ለተሰጡለት ትምህርት በሙሉ ልብ የታዘዙ በመሆናቸው ሐዋርያው ጳውሎስ እግዚአብሔር የተመሰገነ ይሁን በማለት ሳይደመድም የሮሜ ክርስቲያኖችን የመታዘዝ ውጤት ነገረን ከኃጢአት ነጻ ወጥታችሁ የጽድቅ ባርያዎች ሆናችኋል ሲላቸው እንመለከታለን ለእግዚአብሔር ሕግ መታዘዝ ሌላ የተለየ መታዘዝን ብቻ የሚያስከትል ሳይሆን ለተለየ ውጤትም የሚያበቃ ነው ለእግዚአብሔር ሕግ ከልብና ሙሉ የሆነ መታዘዝን በምናደርግበት ጊዜ ከኃጢአት ነጻነት ወጥተን የጽድቅ ባርያዎች መሆን እንጀምራለን ወገኖቼ የጽድቅ ባርያ ብቻ ሳይሆን  ከኃጢአት ነጻ መውጣት በራሱ የሚቻለው ለእግዚአብሔር ሕግ ከመታዘዝ የተነሳ ነው ለዚህ ነው መጽሐፍቅዱሳችን በገላትያ 5 13 ላይ ወንድሞች ሆይ፥ እናንተ ለአርነት ተጠርታችኋልና፤ ብቻ አርነታችሁ ለሥጋ ምክንያትን አይስጥ፥ ነገር ግን በፍቅር እርስ በርሳችሁ እንደ ባሪያዎች ሁኑ የሚለን በመሆኑም እርስ በእርስ በፍቅር ባርያዎች ወደምንሆንበት ሕይወት ውስጥ የምንገባው በቅድሚያ ወደ ተጠራንበት አርነት ስንመጣና በዚሁ በቃሉ  አርነት ስንወጣ ነው አለበለዚያ ግን ባርነቱ የፍቅር መሆኑ ይቀርና የሌላ ይሆናል ይህ በሚሆንበት ጊዜ ደግሞ በነጻነት ልንኖር ክርስቶስ የሰጠንን ነጻነት ሳይቀር የሚጋፋ ይሆንና እንደገና ወደ ከፋ ባርነት ውስጥ ይከተናል ለዚህ ነው ሐዋርያው አሁንም ጸንታችሁ ቁሙ እንደገናም በባርነት ቀንበር አትያዙ ሲል የመከረን ይህን ማለቱ ግን አርነታችሁ ለሥጋ ምክንያት ይስጥ ማለቱ እንዳልሆነ ለሁላችንም ግልጽ ሊሆን ይገባል ስለዚህ አንዳንዴም አስተውለን ብቻ ሳይሆን ባለማስተዋልና የቃሉን እውነትም እንደሚገባ ባለመረዳት በባርነት ቀንበር መያዝ አለ ገላትያ 5 1 ለአርነት የተጠራ ሰው ተቀዳሚና መጀመርያ የሆነውን አርነቱን የሚያገኘው በእግዚአብሔር ቃል ነው በዮሐንስ ወንጌል 8 31 _ 37 ላይ ሄደን ስንመለከት ኢየሱስም ያመኑትን አይሁድ እናንተ በቃሌ ብትኖሩ በእውነት ደቀ መዛሙርቴ ናችሁ እውነትንም ታውቃላችሁ እውነትም አርነት ያወጣችኋል አላቸው እነርሱም መልሰው የአብርሃም ዘር ነን ለአንድም ስንኳ ከቶ ባሪያዎች አልሆንም፤ አንተ አርነት ትወጣላችሁ እንዴት ትላለህ ? አሉት ኢየሱስ መለሰ፥ እንዲህ ሲል፦ እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ኃጢአት የሚያደርግ ሁሉ የኃጢአት ባርያ ነው ባርያም ለዘላለም በቤት አይኖርም፤ ልጁ ለዘላለም ይኖራል እንግዲህ ልጁ አርነት ቢያወጣችሁ በእውነት አርነት ትወጣላችሁ የአብርሃም ዘር መሆናችሁንስ አውቃለሁ ነገር ግን ቃሌ በእናንተ አይኖርምና ልትገድሉኝ ትፈልጋላችሁ እንግዲህ አርነት መውጣት የሚቻለው አንድና አንድ በሆነው በእግዚአብሔር ቃል ብቻ ነው የእነ እገሌ ዘር ነኝ የእነርሱ ደቀመዝሙር ነበርኩ በእነርሱ ሥር ነው ተኮትኩቼ ያደኩት ከልጅነቴ ዘመን ጀምሮ እንዲህና እንዲያ ነኝ በማለት አርነት አይመጣም የታወቁ ስመጥር አገልጋዮችና የተቀቡ የእግዚአብሔር ሰዎች ሌላም ሌላም ልንል እንችላለን እሰየው መልካም ነው አርነት ግን የሚገኘው የእግዚአብሔርን ቃል በማመንና በማወቅ ብሎም ያመነውንና ያወቅነውን ቃል በመታዘዝ ነው ከዚህ ውጪ ግን ሥራችን ይመሠክርብናልና አርነት የለም ቃሉ በሌለበት ሰው ውስጥ ያለው የአብርሃም ዘር ነን ለአንድም ስንኳ ባሮች አልሆንም ባሉት በአይሁድ ውስጥ እንደነበረው ዓይነት  ቅናት ጥል ክርክር ዛቻ ግድያና የመሣሠሉት ነገር ነው ያለው ከዚህ በመቀጠል በራዕይ መጽሐፍ ላይ የእግዚአብሔር ሕዝብ ሥዕል ምን እንደሚመስል እንመለከታለን በራዕይ 14 12 ላይ የእግዚአብሔርን ትእዛዛት የሚጠብቁት ኢየሱስንም በማመን የሚጸኑት ቅዱሳን ትዕግሥታቸው በዚህ ነው ይለናል መጽሐፍቅዱሳችንን አውጥተን ስንመለከት ደግሞ ቤተክርስቲያን ታዋቂ ድርጅትና ትልቅ ዲኖሚኔሽን አይደለችም ክርስቶስ ስለዚችው ቤተክርስቲያን ሲናገር አንተ ታናሽ መንጋ መንግሥትን ሊሰጣችሁ የአባታችሁ በጎ ፈቃድ ነውና አትፍሩ ነው ያለው የሉቃስ ወንጌል 12 32 እንደገናም በጠበበው ደጅ ግቡ፤ ወደ ጥፋት የሚወስደው ደጅ ሰፊ፥ መንገዱም ትልቅ ነውና፥ ወደ እርሱም የሚገቡ ብዙዎች ናቸው ወደ ሕይወት የሚወስደው ደጅ የጠበበ፥ መንገዱም የቀጠነ ነውና፥ የሚያገኙትም ጥቂቶች ናቸው አለን የማቴዎስ ወንጌል 7 13 እና 14 እንመልከት በያዕቆብ መጽሐፍ ላይ ደግሞ አመንዝሮች ሆይ ዓለምን መውደድ ለእግዚአብሔር ጥል እንዲሆን አታውቁምን ? እንግዲህ የዓለም ወዳጅ ሊሆን የሚፈቅድ ሁሉ የእግዚአብሔር ጠላት ሆኖአል ይለናል ያዕቆብ 4 4 በውጤቱም ይህንን ዓለም የሚከተሉ ሰዎች በትክክለኛው በሰይጣን ዓለም ውስጥ ናቸውና ለእነርሱም የእግዚአብሔር ምሳሌ የሆነ የክርስቶስ የክብሩ ወንጌል ብርሃን እንዳያበራላቸው የዚህ ዓለም አምላክ የማያምኑትን ሃሳብ አሳወረ በማለት ተናገረን 2 ቆሮንቶስ 4 4 እንደገናም ከእግዚአብሔር እንደሆንን ዓለምም በክፉ እንደተያዘ እናውቃለን ይለናል 1 ዮሐንስ መልዕክት 5 19 ጌታ እግዚአብሔር በምናነበው ቃል ያሳድገን ሕይወታችንንም  ይለውጥልን


የቃሉ አገልጋይ ቄስ ዮናስ ጌታነህ

Thursday, April 2, 2015

የሚመራ መፈለግ Seeking guidance ክፍል አንድ

የሚመራ መፈለግ


Seeking guidance


ክፍል አንድ


ይህ Joshua Breakthrough Renewal Teaching and Preaching Ministry ሥር እየተዘጋጀ የሚቀርብላችሁ ትምህርት ነው

ፊልጶስም ሮጦ የነቢዩን የኢሳይያስን መጽሐፍ ሲያነብ ሰማና በውኑ የምታነበውን ታስተውለዋለህን ? አለው
እርሱም፦ የሚመራኝ ሳይኖር ይህ እንዴት ይቻለኛል ? አለው

የሐዋርያት ሥራ  8 30 እና 31


ወጥቶም ከእርሱ ጋር ይቀመጥ ዘንድ ፊልጶስን ለመነው ያነበውም የነበረ የመጽሐፉ ክፍል ይህ ነበረ፤ እንደ በግ ወደ መታረድ ተነዳ፥ የበግ ጠቦትም
በሸላቹ ፊት ዝም እንደሚል፥ እንዲሁ አፉን አልከፈተም በውርደቱ ፍርዱ ተወገደ፤ ሕይወቱ ከምድር ተወግዳለችና ትውልዱንስ ማን ይናገራል ?
ጃንደረባውም ለፊልጶስ መልሶ፦ እባክህ፥ ነቢዩ ይህን ስለ ማን ይናገራል ? ስለ ራሱ ነውን ? ወይስ ስለ ሌላ ? አለው ፊልጶስም አፉን ከፈተ፥ ከዚህም
መጽሐፍ ጀምሮ ስለ ኢየሱስ ወንጌልን ሰበከለት በመንገድም ሲሄዱ ወደ ውኃ ደረሱ፤ ጃንደረባውም  እነሆ ውኃ፤ እንዳልጠመቅ የሚከለክለኝ
ምንድር ነው ? አለው ፊልጶስም  በፍጹም ልብህ ብታምን፥ ተፈቅዶአል አለው መልሶም ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ አምናለሁ
አለ ሰረገላውም ይቆም ዘንድ አዘዘ፥ ፊልጶስና ጃንደረባው ሁለቱም ወደ ውኃ ወረዱ፥ አጠመቀውም ከውኃውም ከወጡ በኋላ የጌታ መንፈስ ፊልጶስን
ነጠቀው፤ ጃንደረባውም ሁለተኛ አላየውም፥ ደስ ብሎት መንገዱን ይሄድ ነበርና

      
የሐዋርያት ሥራ  8 32 _ 39


በግልጽነት  ከእግዚአብሔር አገልጋይ እርዳታን መፈለግ ዋነኛውን የእግዚአብሔርን ቃል ለመረዳት ይጠቅማል ስለዚህ ጉዳይ ጳውሎስ የተናገረው ነገር አለ  እንግዲህ ያላመኑበትን እንዴት አድርገው ይጠሩታል ? ባልሰሙትስ እንዴት ያምናሉ ?  ያለ ሰባኪስ እንዴት ይሰማሉ ?  መልካሙን የምሥራች የሚያወሩ እግሮቻቸው እንዴት ያማሩ ናቸው ተብሎ እንደ ተጻፈ ካልተላኩ እንዴት ይሰብካሉ ? ይለናል ሮሜ 10 14 _ 15 እንደገናም ጴጥሮስን እኔም እልሃለሁ፥ አንተ ጴጥሮስ ነህ፥ በዚችም ዓለት ላይ ቤተ ክርስቲያኔን እሠራለሁ፥ የገሃነም ደጆችም አይችሉአትም አለው የማቴዎስ ወንጌል 16 28 ደቀመዛሙርቱን በአንድ ላይ ደግሞ እንግዲህ ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው፥ ያዘዝኋችሁንም ሁሉ እንዲጠብቁ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው፤ እነሆም እኔ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር ነኝ በማለት መመርያ ሰጣቸው የማቴዎስ ወንጌል 28 ፥ 19 እና 20 ቤተክርስቲያን የእግዚአብሔር ቃል እውነትን ለማስተማር ሃላፊነት አለባት እያንዳንዱ በግሉ ደግሞ ቤተክርስቲያን የምታስተምረውን ሊሰማ ሃላፊነት አለበት ቤተክርስቲያን ሕንጻ አይደለችም ወይም የምትታይ ድርጅትም አይደለችም ነገር ግን እንደ ሕዝብ በእግዚአብሔር መንፈስ የምትመራ ናት የሕዝቦች ሕብረት የሚረዳው ደግሞ ኢየሱስ ክርስቶስ የተናገረውን መንፈሳዊ እውነት ለመማር ነው በዚህ ውስጥ ግን ጌታ ሁሉን ፈትኑ መልካሙን ያዙ ብሎናል 1 ተሰሎንቄ 5 23 ይህንን ጉዳይ በተመለከተ ሐዋርያው ጳውሎስ ቲቶን እንዲህ ሲል ይናገረዋል ስለዚህ ምክንያት የቀረውን እንድታደራጅ በየከተማውም፥ እኔ አንተን እንዳዘዝሁ፥ ሽማግሌዎችን እንድትሾም በቀርጤስ ተውሁህ የማይነቀፍና የአንዲት ሚስት ባል የሚሆን፥ የሚያምኑም ልጆች ያሉት፥ ስለ መዳራትም ወይም ስለ አለመታዘዝ የማይከሰስ ማንም ቢኖር፥ ሹመው ኤጲስ ቆጶስ፥ እንደ እግዚአብሔር መጋቢ፥ የማይነቀፍ ሊሆን ይገባዋልና፤ የማይኮራ፥ የማይቆጣ፥ የማይሰክር፥ የማይጨቃጨቅ፥ ነውረኛ ረብ የማይወድ ነገር ግን እንግዳ ተቀባይ፥ በጎ የሆነውን ነገር የሚወድ፥ ጠንቃቃ፥ ጻድቅ፥ ቅዱስ፥ ራሱን የሚገዛ ይሁን ሕይወት በሚገኝበት ትምህርት ደግሞ ሊመክር ተቃዋሚዎቹንም ሊወቅስ ይችል ዘንድ፥ እንደተማረው በታመነ ቃል ይጽና የማይታዘዙና ከንቱ የሚናገሩ የሚያታልሉ ይልቁንም ከተገረዙት ወገን የሚሆኑ ብዙ ናቸውና ቲቶ 1 5 _ 9 ስለ ሐሰተኛ ነቢያትም የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ሲል ይናገራል የበግ ለምድ ለብሰው ከሚመጡባችሁ በውሥጣቸው ግን ነጣቂዎች ተኵላዎች ከሆኑ ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ ከፍሬያቸው ታውቋቸዋላችሁ ከእሾህ ወይን ከኩርንችትስ በለስ ይለቀማልን ? ይለናል እንደገናም በዚያ ቀን ብዙዎች ጌታ ሆይ፥ ጌታ ሆይ፥ በስምህ ትንቢት አልተናገርንምን፥ በስምህስ አጋንንትን አላወጣንምን፥ በስምህስ ብዙ ተአምራትን አላደረግንምን ?  ይሉኛል የዚያን ጊዜም ከቶ አላወቅኋችሁም፤ እናንተ ዓመፀኞች፥ ከእኔ ራቁ ብዬ እመሰክርባቸዋለሁ ይለናል የማቴዎስ ወንጌል 7 15 _ 16 22 _ 23 እንመልከት ስለዚህ የነቢያትን ቃል የምንፈትንበት የእግዚአብሔር ቃል አለን መጽሐፉ ሲናገር እንዲህ ይላል የእግዚአብሔር ቃል ሁሉ ተፈትናለች እርሱ ለሚታመኑት ጋሻ ነው እንዳይዘልፍህ፥ ሐሰተኛም እንዳትሆን በቃሉ አንዳች አትጨምር ይለናል እንደገናም ወደ ሕግና ወደ ምስክር ሂዱ፦ እንዲህም ያለውን ቃል ባይናገሩ ንጋት አይበራላቸውም ምሣሌ 30 5 - 6 ኢሳይያስ 8 20 እግዚአብሔር አምላክ በምናነበው ቃል ብዙ የሆነ መረዳቱን ይስጠን የክፍል ሁለት ትምህርት ይቀጥላል ተባረኩልኝ





ቀሲስ አባ ዮናስ ጌታነህ ነኝ