Saturday, June 6, 2015

ሁሉንም መጻሕፍት በባለቤትነት እንመልከት Look at all the Scriptures on the Subjects ክፍል አራት

ሁሉንም መጻሕፍት በባለቤትነት እንመልከት

Look at all the Scriptures on the Subjects

ክፍል አራት


በአንድ የእግዚአብሔር ቃል ጥናት ላይ ወደ ውሳኔ ከመምጣታችን በፊት ጊዜ ወስደን ጥሩ የሆነ መረዳት እንዲኖረን ከባለቤቱ ጋር የተገናኙ ጥቅሶችን ማየት ያስፈልገናል በሐዋርያት ሥራ 28 23 ላይ ቀንም ቀጥረውለት ብዙ ሆነው ወደ መኖሪያው ወደ እርሱ መጡ፤ ስለ እግዚአብሔር መንግሥትም እየመሰከረ ስለ ኢየሱስም ከሙሴ ሕግና ከነቢያት ጠቅሶ እያስረዳቸው፥ ከጥዋት ጀምሮ እስከ ማታ ድረስ ይገልጥላቸው ነበር ይለናል ከሐዋርያው ጳውሎስ  የቃሉ አገልግሎትና መረዳት ተምሣሊትነት እንደምናየው ተገቢ ወደሆነ መረዳት ለመምጣት ከባለቤቱ ጋር የተገናኙ ጽሑፎችን በእርግጠኝነት ወደ ሂሳብ ማምጣቱ ነው ይህ ታድያ መንፈሳዊ ነገሮችን ከመንፈሳዊ ነገር ጋር የማነጻጸር መመርያ ነው በ1ኛ ቆሮንቶስ 2 13 ላይ መንፈሳዊውን ነገር ከመንፈሳዊው ነገር ጋር አስተያይተን መንፈስ በሚያስተምረን ቃል ይህን ደግሞ እንናገራለን እንጂ የሰው ጥበብ በሚያስተምረን ቃል አይደለም ይለናል ጳውሎስ ያደረገው ይህንን ነው መንፈሳዊውን ነገር ከመንፈሳዊው ነገር ጋር አስተያየ ማለት ስለ እግዚአብሔር መንግሥትም እየመሰከረ ስለ ኢየሱስ ሊናገር በወደደ ጊዜ ከሙሴ ሕግና ከነቢያት ጠቅሶ እያስረዳቸው፥ ከጥዋት ጀምሮ እስከ ማታ ድረስ መግለጡ በእርግጥም መንፈሳዊውን ነገር ከመንፈሳዊው ነገር ጋር ማስተያየቱን ያመላክታል ታድያ ሁሉንም መጻሕፍት በባለቤትነት ስንመለከት እኛም እንደ ጳውሎስ ሌሎችን እንደዚህ በምልአትና በሰፋ መልኩ ማስረዳት እንጀምራለን ሌላው ሁሉንም መጻሕፍት በባለቤትነት የምንመለከትበት ምክንያት ቅዱሳት መጻሕፍት በእግዚአብሔር መንፈስ የተጻፉ ናቸው ከዚህም ሌላ እነዚህ መጻሕፍት በሰው ፈቃድ የመጡ አይደሉም እና እርስ በእርሳቸው የሚጋጩ አይሆኑም ደግሞም አይጋጩም 2 ጴጥሮስ 1 20 እና 21 የናዝሬቱ ኢየሱስም ጳውሎስ የተጠቀመበትን መንገድ ተጠቅሞ ስለነበር ከሙሴና ከነቢያት ሁሉ ጀምሮ ስለ እርሱ በመጻሕፍት ሁሉ የተጻፈውን ተረጎመላቸው ይለናል የሉቃስ ወንጌል 24 27 ጌታችን ታድያ ይህን ማድረጉ ሁሉንም መጻሕፍት በባለቤትነት መመልከቱን የሚያሳየን ነው እንደገናም በዚሁ በሉቃስ ወንጌል 24 44 _ 48 ላይ እርሱም፦ ከእናንተ ጋር ሳለሁ በሙሴ ሕግና በነቢያት በመዝሙራትም ስለ እኔ የተጻፈው ሁሉ ይፈጸም ዘንድ ይገባል ብዬ የነገርኋችሁ ቃሌ ይህ ነው አላቸው በዚያን ጊዜም መጻሕፍትን ያስተውሉ ዘንድ አእምሮአቸውን ከፈተላቸው እንዲህም አላቸው፦ ክርስቶስ መከራ ይቀበላል በሦስተኛውም ቀን ከሙታን ይነሣል በስሙም ንስሐና የኃጢአት ስርየት ከኢየሩሳሌም ጀምሮ በአሕዛብ ሁሉ ይሰበካል ተብሎ እንዲሁ ተጽፎአል እናንተም ለዚህ ምስክሮች ናችሁ ይላቸዋል ይልቁንም ካኖናይዝድ ሆነው ማለት ቅዱሳት መጻሕፍት ተብለውና በአንድ ላይ ተቆጥረው በአንድ ጥራዝ ውስጥ የገቡ ቢሆኑም እንኳ የተጻፉበት ክፍለ ዘመን ግን ልዩ ልዩ ነው ነገር ግን እጅግ የሚደንቀው ነገር በእግዚአብሔር መንፈስ የተጻፉ ናቸውና እርስ በእርሳቸው ካለመጋጨታቸው የተነሳ አንዱ ለሌላው የማመሳከርያ መንገድና ማቆራኛ ሆነው የቀረቡ ናቸው ለዚህ ነው እንግዲህ ጌታችን ኢየሱስም ሆነ ጳውሎስ ሁሉንም መጻሕፍት በባለቤትነት የተመለከቷቸው በመሆኑም  ለተነሱበት ሃሳብ እንደ ተጨማሪ ማብራርያ ሊጠቀሙባቸው መጻሕፍቱን ሲያጣቅሱና ሲተረጉሙዋቸው የምንመለከተው  ከዚህ የተነሳ ነው ታድያ እነዚህ መጻሕፍት በመንፈስቅዱስ አማካኝነት እንዲጻፉና እንዲደረሱ ላደረገ ለእግዚአብሔር መንፈስቅዱስ ከዘላለም እስከ ዘላለም ክብር ይሁን ከምንል በቀር የምንለው የለም ለአንድ መሠረታዊ ትምህርት አስረጂ እንዲሆኑ ሁሉም መጻሕፍት በባለቤትነት ቀርበው በሚጠቀሱ ጊዜ ሰዎች ዛሬም እንደከበረው ቴዎፍሎስ እርግጡን ያውቃሉ የሉቃስ ወንጌል 1 1 _ 4 ጢሞቴዎስ እንደ ተባለም ክርስቶስ ኢየሱስን በማመን፥ መዳን የሚገኝበትን ጥበብ ሊሰጡአቸው የሚችሉትን ቅዱሳን መጻሕፍትን ሁሉ ያውቃሉ ከማን እንደተማሩም አውቀው ደግሞ በተማሩበትና በተረዱበት ነገርም ጸንተው ይኖራሉ እንግዲህ ሁሉንም መጻሕፍት በባለቤትነት መመልከት ለተነሳንበትም መሠረታዊ የእግዚአብሔር ቃል ሃሳብ እነዚህኑ መጻሕፍት በአስረጂነት ማቅረብ ጥቅሙ ያለው እዚህ ላይ ነው እና ቅዱሳን የእግዚአብሔር ወገኖች ይህንን የእግዚአብሔር ቃል እውነት እንወቅ አውቀንም ደግሞ እንጠቀምበት እላችኋለሁ ከዚህም ሌላ የመጽሐፍቅዱስ መንፈሳዊ ሥነፍጥረት ወይንም መንፈሳዊ ተፈጥሮ የተገለጸው በኤፌሶን ፲፯ ላይ ነው ቃሉም እንዲህ ይለናል የመዳንንም ራስ ቁር የመንፈስንም ሰይፍ ያዙ እርሱም የእግዚአብሔር ቃል ነው
The Spiritual nature of the bible is described in Ephesians 6 : 17 as << The sword of Spirit, which is the word of God >>

Thank u God bless u all People of God


The servant of God Yonas Asfaw 

Wednesday, June 3, 2015

Joshua Tehadso: ዓረፍተ ነገሩ ወይም የየምዕራፉ አንቀጽ የተጻፈበት ሃሳቡን መመርመር Con...

Joshua Tehadso: ዓረፍተ ነገሩ ወይም የየምዕራፉ አንቀጽ የተጻፈበት ሃሳቡን መመርመር Con...: ዓረፍተ ነገሩ ወይም   የየምዕራፉ አንቀጽ የተጻፈበት ሃሳቡን   መመርመር Consider the Context ክፍል ሦስት የመጽሐፍቅዱሱን ክፍል ዓረፍተ ነገሩ የተጻፈበትን ከላይና ከታ...

ዓረፍተ ነገሩ ወይም የየምዕራፉ አንቀጽ የተጻፈበት ሃሳቡን መመርመር Consider the Context ክፍል ሦስት

ዓረፍተ ነገሩ ወይም  የየምዕራፉ አንቀጽ የተጻፈበት ሃሳቡን  መመርመር

Consider the Context

ክፍል ሦስት


የመጽሐፍቅዱሱን ክፍል ዓረፍተ ነገሩ የተጻፈበትን ከላይና ከታች አስተውሎ ማጥናት ተገቢ ነው ለምን ? ስንል ከዓረፍተ ነገሩ ውጪ ማለት ዓረፍተ ነገሩን በጥቂቱ በዙርያው ያለውን ነገር ሳያዩ በመመልከት ወይንም ጥቅስ ቆንጥሮ በማንሳት የተሳሳተ ትርጉም መያዝና ወደከፋ ስሕተት ውስጥም መግባት ስለ አለ ነው በዘፍጥረት 3 4 እና 5 ላይ እባብም ለሴቲቱ አላት ሞትን አትሞቱም ከእርስዋ በበላችሁ ቀን ዓይኖቻችሁ እንዲከፈቱ እንደ እግዚአብሔርም መልካምንና ክፉን የምታውቁ እንድትሆኑ እግዚአብሔር ስለሚያውቅ ነው እንጂ አለ ይህንን ውሸት የተናገረው ሰይጣን ነው እርሱም ያለው ሰው አይሞትም ነው ትክክለኛው ትምህርት ግን ከእግዚአብሔር ጋር የተገናኘ በመሆኑ በዘፍጥረት 2 16 እና 17 ላይ እግዚአብሔር አምላክም ሰውን እንዲህ ብሎ አዘዘው፦ ከገነት ዛፍ ሁሉ ትበላለህ ነገር ግን መልካምንና ክፉን ከሚያስታውቀው ዛፍ አትብላ ከእርሱ በበላህ ቀን ሞትን ትሞታለህና ሲለው እንመለከታለን ታድያ በዘፍጥረት መጽሐፍ ምዕራፍ 3 4 ላይ እባብም ለሴቲቱ አላት ሞትን አትሞቱም ተብሎ በተጻፈው ቃል መሠረት  ሰይጣን ሞትን አትሞቱም እያለ ቢናገርም ጌታ እግዚአብሔር በዚሁ በቃሉ  በዘፍጥረት 2 16 እና 17 ላይ ሞትን ትሞታለህ ሲል ተናግሯል ሕያውነታችንንም ለማረጋገጥ እነዚህን ጥቅሶች ይጽፋል 1 ጢሞቴዎስ 6 14 _ 16 ሮሜ 2 7 1 ቆሮንቶስ 15 53 ለዚህ ነው እንግዲህ የተጻፈበትን አውድ ጠብቀን ዓረፍተ ነገሩ የተጻፈበትን ክፍል ከላይና ከታች እንዲሁም ከጠቅላላው የመጽሐፍቅዱስ ቃል ጋር በማገናኘት ተገቢ የሆነውን ትርጉም ሳናገኝ ወይንም ለጊዜው የሚሆነንን ጥቅስ ቆንጥረን በመነሳት ብቻ የተጻፈበትን ሳንመረምር እንዲሁ በተለምዶ ወይንም መስሎን ይህ ማለት እንዲህና እንዲያ ነው ስንል መናገርም ሆነ መተርጎም የማይገባን አንዳንድ ጊዜ ጠቅላላውን ምዕራፍ በማንበብ ባለቤቱን ማግኘት እንችላለን የማቴዎስ ወንጌል 7 18 እና 19 እንመልከት ስለሚበሉና ስለማይበሉ ምግቦች ደግሞ የእግዚአብሔር ቃል በግልጽ ይናገራል ዘሌዋውያን ምዕራፍ 11 በሙሉ እንደገናም ዘዳግም ምዕራፍ 14 በሙሉ ልንመለከት እንችላለን ነገር ግን በማርቆስ ወንጌል 7 5 ላይ የምንባቡ ሃሳብ የገለጠው ትክክለኛውን ትርጉም ነው መጽሐፉ የሚጠይቀን ደቀመዛሙርቱ ለምን በሽማግሌዎች ወግ አልሄዱም ? ሆኖ  ነገር ግን እጃቸውን ሳይታጠቡ እንጀራ በሉ የሚል ሃሳብ የያዘ ነው በተመሣሣይ ሃሳብ የማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ 15 በሙሉ እና ከቁጥር 19  እስከ 20 ያሉትን ሃሳቦች በመመልከት የሃሳቡ ሙሉ መልስ ያለው በእነዚህ ቁጥሮች ውስጥ መሆኑን እናስተውላለን ነገር ግን በዚህ አጋጣሚ ለአንባቢዎቼ  ማስተላለፍ  የምፈልገው እነዚህን የጠቀስኳቸውን ምዕራፍና ቊጥሮች መጽሐፍቅዱሳችሁን ከፍታችሁ በተገቢው መልኩ ካላነበባችኋቸውና ካልተመለከታችኋቸው የትምህርቱ ሃሳብ ምን እንደሆነና ሃሳቡም ማንንና ምንን ለመግለጽ እንደተፈለገ ሊገባችሁ አይችልም ስለዚህ በተቻለ መጠን መጽሐፍቅዱሳችሁን አውጥታችሁ በማንበብ እና በመጠቀም ይህንን ትምህርት እንድታጠኑት ይሁን እላለሁ ተባረኩልኝ ከዚህም ሌላ በሮሜ 9 30 _ 32 ላይ እንግዲህ ምን እንላለን ? ጽድቅን ያልተከተሉት አሕዛብ ጽድቅን አገኙ፥ እርሱ ግን ከእምነት የሆነ ጽድቅ ነው እስራኤል ግን የጽድቅን ሕግ እየተከተሉ ወደ ሕግ አልደረሱም ይህስ ስለ ምንድር ነው ? በሥራ እንጂ በእምነት ጽድቅን ስላልተከተሉ ነው፤ እነሆ፥ በጽዮን የእንቅፋት ድንጋይና የማሰናከያ ዓለት አኖራለሁ በእርሱም የሚያምን አያፍርም ተብሎ እንደ ተጻፈ በእንቅፋት ድንጋይ ተሰናከሉ ይለናል ይህንን የቃሉን እውነታ አስተውለን  ስንመለከተው እስራኤል ወደ ሕግ አይድረሱ እንጂ ሕጉ ግን ንጹሕና ቅዱስ ፍጹምም ነው ስለዚህ በሮሜ 7 12 እና 13 ላይ ስለዚህ ሕጉ ቅዱስ ነው ትእዛዚቱም ቅድስትና ጻድቅት በጎም ናት እንግዲህ በጎ የሆነው ነገር ለእኔ ሞት ሆነብኝን ? አይደለም፥ ነገር ግን ኃጢአት ሆነ፤ ኃጢአትም በትእዛዝ ምክንያት ያለ ልክ ኃጢአተኛ ይሆን ዘንድ፥ ኃጢአትም እንዲሆን ይገለጥ ዘንድ በጎ በሆነው ነገር ለእኔ ሞትን ይሠራ ነበር ይለናል እግዚአብሔር የምናነበውን ቃል እንድናስተውለውና እንድንጠቀምበት ይርዳን አሜን
 

 ቀሲስ ዮናስ ጌታነህ