Seeking Guidance የሚመራ መፈለግ በመታዘዝ የሚመጡ ብዙ ትርፎች በበራችን ላይ በፍጥነት ለእኛ ይገለጣሉ ክፍል ስድስት
Seeking Guidance
የሚመራ መፈለግ
በመታዘዝ የሚመጡ ብዙ ትርፎች በበራችን ላይ በፍጥነት ለእኛ ይገለጣሉ
ክፍል ስድስት
የእግዚአብሔር ቃል በመዝሙር 34 ፥ 8 ላይ እግዚአብሔር ቸር እንደሆነ ቅመሱ እዩም በእርሱ የሚታመን ሰው ምስጉን ነው አለ ስለዚህ የእግዚአብሔርን ቸርነት ለመቅመስየእግዚአብሔርን ቃል መታዘዝ አማራጭ የሌለው ነገር ነው በ1ኛ ዮሐንስ 3 ፥ 22 ላይ የእግዚአብሔር ቃል የሚለን እንደዚህ ነው ወዳጆች ሆይ ልባችን ባይፈርድብን በእግዚአብሔርዘንድ ድፍረት አለን ትእዛዙንም የምንጠብቅና በፊቱ ደስ የሚያሰኘውን የምናደርግ ስለሆንን የምንለምነውን ሁሉ ከእርሱ እናገኛለን ይለናል በመሆኑም እንግዲህ ለቃሉ በመታዘዝ ውስጥየሚፈለገው ነገር ሁሉ ከተገኘ በመታዘዝ የሚመጡ ብዙ ትርፎች እንዳሉን በዚሁ በተገለጠው በእግዚአብሔር ቃል መረዳት እንችላለን በትንቢተ ሚልክያስ 3 ፥ 10 ላይም በቤቴ ውስጥመብል እንዲሆን አሥራቱን ሁሉ ወደ ጎተራ አግቡ የሰማይንም መስኮት ባልከፍትላችሁ በረከትንም አትረፍርፌ ባላፈስላችሁ በዚህ ፈትኑኝ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር ይለናል እኛ ጌታ በሚያዘን ነገር ሁሉ ታማኞች ሆነን ለቃሉ ከታዘዝን እግዚአብሔር በረከቱን ሁሉ ሊያፈስልን የታመነ ነው ለዚህ ነው ጌታ ኢየሱስም እኔ ሕይወት እንዲሆንላቸው እንዲበዛላቸውመጣሁ ያለው ዮሐንስ ወንጌል 10 ፥ 10 የሚበዛ ሕይወት ቃሉን ከመታዘዝ የተነሳ በእግዚአብሔር በረከት የተጎበኘና የተጥለቀለቀ ሕይወት ነው ስለዚህም በመዝሙር 111 ፥ 10 ላይየጥበብ መጀመርያ እግዚአብሔርን መፍራት ነው ለሚያደርጓትም ደኅና ማስተዋል አላቸው ምስጋናውም ለዘላለም ይኖራል ይለናልና እግዚአብሔርን ፈርተን የእግዚአብሔርን ቃልበማስተዋል ብናደርግ ማለት ብንታዘዝ በረከታችንም ሆነ ማስተዋላችን በዚያው ልክ እየጨመረ ይመጣል ጌታ እግዚአብሔር በዚህ በረከት ይባርከን ከዚህ በመቀጠል ከዚሁ ጋር የተያያዘጥቂት ሃሳቦችን በእንግሊዝኛ ለማቅረብ እወዳለሁ ይህን የማደርገው ሃሳቡን ይበልጥ ስለሚደግፍልኝና የተሻለ ማብራርያ ስለሚሰጠው ነው
Obey God's Word AND Prove it right
Put God's word to the test by practicing the things you are learning Acknowledge how his ways bring positive change in your life. The best way to determine that God's commands and teachings bring true peace and blessings is by living them.
God bless all People of God
God servant Preacher and Teacher Yonas Asfaw
No comments:
Post a Comment